Kesis Asteraye Nigatu with Ethiopian Orthodox Tewahedo Church Both Synod peace delegation In Washington DC
Synod peace delegation DC 2010
[img src=http://medhanialemeotcks.org/wp-content/flagallery/synod-peace-delegation-dc-2010/thumbs/thumbs_dscn2673.jpg]
[img src=http://medhanialemeotcks.org/wp-content/flagallery/synod-peace-delegation-dc-2010/thumbs/thumbs_dscn2671.jpg]
[img src=http://medhanialemeotcks.org/wp-content/flagallery/synod-peace-delegation-dc-2010/thumbs/thumbs_dscn2658.jpg]
[img src=http://medhanialemeotcks.org/wp-content/flagallery/synod-peace-delegation-dc-2010/thumbs/thumbs_dscn2654.jpg]
[img src=http://medhanialemeotcks.org/wp-content/flagallery/synod-peace-delegation-dc-2010/thumbs/thumbs_img_0721.jpg]
[img src=http://medhanialemeotcks.org/wp-content/flagallery/synod-peace-delegation-dc-2010/thumbs/thumbs_img_0731.jpg]
የሆሳዕና በዓል ለረዥም ዘመናት እየተመላለሰ በተከበረበት ዘመን ያልተከሰቱ በዘንድሮው ሆሳዕና ብቻ በወያኔ መንግሥት የተደረጉ አሰቃቂ ክስተቶች – በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
መግቢያ
በኢትዮጵያ ታሪክ በዓላቶቻችን፤ የገባር ወንዞችን ውሀ እያግበሰበሰ እንደሚጓዘው ዓባይ ወንዛችን፤ በወራት ታዝለው የኡደታቸውን ሂደት በመፈጸም ላይ ሳሉ የሚገጥሟቸውን ክስተቶች እየሰበሰቡ የሚቀጥሉ ናቸው። ክስተቶችም ደስታችንና ሀዘናችንን የምንገልጽባቸው ናቸው። ድርብ በዓላት የሚባል ስምም ተሰጥቷቸውል። ታሪካችንን ሰፊና ጥልቅ ያደረጉት፤ ስነ ጽሑፋችንንም ያዳበሩት አገራችን በዚህ መንገድ በመጓዝ የሰበሰሰበቻቸው ክስተቶች ናቸው። ከውጭ የሚመጣ ጠላትና ከውስጥም የጠላት ወኪል (የባንዳነት ውርስ የተሸከመ የባንዳ ልጅ) ሆኖ የሚሰለፈው መጀመሪያ የሚጋጭ ቀደም ብለው ከነበሩት ክስተቶችን ከተሸከሙት በዓላት ጋራ ነው። ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ፍትሐት – በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
ለአቶ መለስ የተደረገው ፍትሐት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እይታ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ.
ቀራፊ – በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
ቀራፊ ማለት፡ በቤተ ክርስቲያናችን ቋንቋና ሥርአት ለሰሞንና ለሰንበት እንጨት እየለቀሙ፡ እየቆርጡና እየፈለጡ፤ ማይ (ው ) ከወንዝ እየቀዱ፡ በደ ሰላም ለወደቁና ለቤተ ልሄም ለሚያቀርቡ ሰወች የተሰጠ ያገልግሎት ድርሻና መታወቂያ ስም ነው። በንባብ፡ በዜማና በቅኔ ትምህርት ቤት ያሉ ተማሪዎችም አገልግሎቱን ከቀራፊዎች ጋራ በቅጣት መልክ ይጋሩታል። ሰሞኑን በመገናኛ መስመሮች ሲናገሩ የሰነበቱት የነ አቶ ስብ ት ነጋ ንግር ይህን ትዝታ ጭሮብኛል። ከዚህ በታች በዘረዘርኳቸው፡ ቀራፊነት እንዴት ተከሰተ? የነአቶ ስብ ት ነጋ ባህርይስ እንዴት ተመሳሰለ? ዛሬስ እነ አቶ ስብ ት ነጋ ምን እያሉና እያደረጉ ናቸው? በስርአታችንና በየኔታ ፈረደ ቅጣት እንገላገላቸው። በማለት ይህችን ጦማር እንዳዘጋጅ ተገደድኩ።
ለሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መሸኛ – በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
ወንድማችን ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ ሁሉንም ነበሩ!
እንደ ተከበሩ ሰዓሊ ወንድማችን ያለ ተልእኮውን ፈጽሞ ላለፈ ባለሙያ፡ ፈጣሪ ያዘጋጀለትን ሩጫ ጨርሶ ከሚወደው ወገኑ በሞት ሲለይ፡ ስለተደነቀበት ችሎታው ወዳጅ ዘመድ ብቻ ሳይሆን ጠላትም እጅግ ጎልቶ በመታየት ላይ ያለውን ተግባር፡ ከመሰወር ይልቅ ራሱን በሚጠቅመው መንገድ ይናገረዋልና የነ አባ ጳውሎስ በሰዓሊ አፈወርቅ አሸኛኘት ስርዓት ላይ ያደረጉት ንግግር ካብ አይገባ ድንጋይ ነው። ለማንበብ እዚህ ይጫኑ








